Fana: At a Speed of Life!

የምርምር ስራዎች የምርምር ስነምግባር መርሆዎችን ተከትለው እንዲሠሩ የሚያስችል ስልጠናዊ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምርምር ስራዎች የምርምር ስነምግባር መርሆዎችን ተከትለው እንዲሠሩ በተቋማት የሚገኙ የምርምር ስነምግባር ኮሚቴዎችን አቅም መገንባትና ማጠናከር የሚያስችል ስልጠናዊ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

ስልጠናው ከፍተኛ የትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በመሠረታዊ፣ በሳይንስና በጥናትና ምርምር የጎለበቱ እንዲሆኑ የሚያስችል ስልት ለመንደፍ ያስችላል ተብሏል፡፡

ከዚህ ባለፈም የምርምሮቹ ውጤቶች በስራ ላይ የሚውሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ይረዳልም ነው የተባለው፡፡

ስልጠናው ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፥ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡

በሰላማዊት ተስፋዬ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.