Fana: At a Speed of Life!

የምዕራባውያንን ጣልቃ ገብነት የሚቃወም ሰልፍ በዓላማችን ዋና ዋና ከተሞች የፊታችን እሁድ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምዕራባውያን አገራት በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት እና ጫና የሚቃወም ዓለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ የፊታችን እሁድ ሕዳር 12 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተጠቆመ።
ሰልፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግስት ጎን መቆሙን የሚያረጋግጥበት ነው ተብሏል።
የዓለም አቀፉ የተቃውሞ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል አቶ ከባዱ ሙሉቀን ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ ሰልፉ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምዕራባውያን አገራት በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት እንደሚቃወሙ ድምጻቸውን በአንድነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያሰሙበት ነው፡፡
በሰሞኑ በዋሺንግተን ዲሲ፣ቶሮንቶ እና ብራሰልስ ተመሳሳይ ዓላማ ያነገቡ ሰልፎች መካሄዳቸውን አስታውሰው፤ የኢትዮጵያ ድምጽ ጎልቶ እንዲሰማ በማሳብ ዓለም አቀፍ ይዘት ያለው ሰልፍ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
እሁድ ሕዳር 12 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄደው ዓለም አቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ በዓላማችን በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች ላይ እንደሚካሄድ ነው የጠቆሙት።
ዋሺንግተን ዲሲ፣ አትላንታ፣ ኒውዮርክ፣ ቶርንቶ፣ ካልጋሪ፣ ጆሀንስበርግ፣ ቴልአቪቭ፣ ቶኪዮ፣ ሲድኒ፣ ለንደን፣ ኮሎራዶና ቺካጎ እሁድ ሰልፎቹ ከሚካሄድባቸው ከተሞች መካከል ይገኙበታል።
በዕለቱ ሰልፍ የሚካሄድባቸው ሌሎች ከተሞች በቀጣይ ቀናት ይፋ እንደሚሆኑ ነው አቶ ከባዱ የገለጹት።
የጊዜ አቆጣጠርን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ሰላማዊ ሰልፉ በየከተሞቹ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ መካሄድ እንደሚጀምርም ጠቁመዋል።
የዓለም አቀፉ ሰልፍ አካል የሆነው ተቃውሞ በሞንትሪያል እና በኦቶዋ ከተሞች ቅዳሜ ሕዳር 11 ቀን 2014 ዓ.ም እንዲሁም በናሽቪል ከተማ ሕዳር 13 ቀን 2014 ዓ.ም ከተማ እንደሚካሄድም አመልክተዋል።
ሕዳር 16 ቀን 2014 ዓ.ም በጄኔቫ ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ነው ያሉት።
ዓለም አቀፍ ሰልፉ ምዕራባውያን አገራት በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉት ያለውን ጫና እና ጣልቃ ገብነት እንዲሁም ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የሚያስተለልፏቸውን የሐሰት ዘገባዎች እንዲያቆሙ የሚያሳስቡ መልዕክቶች እንደሚተላለፉ መግለጻቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
በሰልፉ ላይ በውጪ አገር የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ከኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግስት ጋር አንድ መሆኑን እንደሚያሳዩም ነው አቶ ከባዱ ያስረዱት።
በሰልፉ ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች እንደሚሳተፉና በተለያዩ ተወካዮች አማካኝነት ንግግሮች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል።
ምዕራባውያን አገራት የኢትዮጵያን እውነት እንዲሰሙና ጣልቃ ገብነታቸውን እንዲያቆሙ ዳያስፖራው ግፊት ማድረጉን ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡
ሕዳር 12 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄደውን ሰላማዊ ሰልፍ ሰላምና አንድነት ማህበር የዋሺንግተን ዲሲ ግብረ ሃይል፣የ#NoMore የትዊተር ዘመቻ እንቅስቃሴ አስተባባሪዎች፣የተለያዩ ተቋማትና አገር ወዳድ ወዳጆች በጋራ እንዳዘጋጁት ተገልጿል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
May be an image of 1 person and text that says 'ዓለም ተቃውሞ ጥቃት አቀፍ ነው! ይሄ ወቅት ኢትዮጵያ ላይ ለአፍሪካ ቀንድ ወሳኝ ጊዜ እየደረሰ ነው። በሁሉም ከተማ የሚገኝ ሁሉም ሰው እንዲሳተፍ ጥያቄ ቀርሏል፡ ሰልፍ በብዙ ዓለም አቀፍ ከተሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ #NoMore ጣልቃ ገብነት እና #NoMore November 21 ሕወሃት እሑድ PM በዲሲ ሰዓት 1:00 ዋይት Pennsylvania ave ሐውስ 1600 Washington,DO @HORNOFAFRICAHUB #NoMore ሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ ማህበር ዋሽንግተን ግብረ ሃይል ከተለያዩ ተቋሞችና አገር ወዳዶች ጋር በመተባበር For info: (202) 556-3078 peaceandunityforethiopia@gmail.com'
0
People reached
0
Engagements
Distribution score
Boost post
Like

Comment
Share
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.