Fana: At a Speed of Life!

የሱዳን ባለሃብቶች የልዑካን ቡድን በትግራይ ክልል ጉብኝት እያደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሱዳን ባለሃብቶች የልዑካን ቡድን በተለያዩ የትግራይ ክልል አካባቢዎች ጉብኝት በማድረግ ላይ ነው፡፡

ልዑኩ ለአንድ ሳምንት በሚኖረው ቆይታ በክልሉ ያሉትን የኢንቨስትመንት አማራጮች ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም በተለያዩ ዘርፎች ባለሃብቶቹ መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ከክልሉ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ነው የተመለከተው።

ባለሀብቶቹ በሱዳን እና በሌሎች መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች የተሰማሩ ናቸው።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.