Fana: At a Speed of Life!

የባህርዳር አውሮፕላን ማረፊያ “የባህርዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ እንዲጠራ ተወሰነ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አመታት “የባህርዳር ግንቦት 20 አውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ ይጠራ የነበረው የባህርዳር አውሮፕላን ማረፊያ”የባህርዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ እንዲጠራ ተወሰነ፡፡

ባለፉት አመታት “የባህርዳር ግንቦት 20 አውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ ይጠራ የነበረው የባህርዳር አውሮፕላን ማረፊያ በህብረተሰቡ ፍላጎት ውይይት ሲደረግበት ቆይቶ ዛሬ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ነው “የባህርዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ” ተብሎ እንዲጠራ የተወሰነው ።

ይህ ስያሜ ከ1983 ዓ.ም በፊትም ይጠራበት እንደነበር ያስታወሰው የከንቲባ ኮሚቴው የህዝቡን ፍላጎትና የከተማውን ወካይ ስያሜ በመምረጥ ስሙ እንዲቀየር በሙሉ ድምፅ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።

ተቋርጦ የነበረው የበረራ አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ አገልግሎቱን እንደሚጀምር አስተባባሪ ኮሚቴው መግለፁን ከአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
1,592
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.