Fana: At a Speed of Life!

የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ  የማህበረሰብ አገልግሎት ስልጠና አላማውን ያሳካ ነው-የስልጠናው አስተባባሪዎችና አሰልጣኞች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)  የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ  የማህበረሰብ አገልግሎት ስልጠና አላማውን ያሳካ መሆኑን  የስልጠናው አስተባባሪዎችና  አሰልጣኞች ተናገሩ  ።

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ  የማህበረሰብ አገልግሎት ሰልጣኞችን እያሰለጠኑ  የሚገኙ ባለሙያዎች÷ ስልጠናው በጎ ፈቃደኞችን  በአስተሳሰብ ፣ በአመለካከትና  በክህሎት  የለወጠ ነው ብለዋል ።

ሰልጣኝ ወጣቶች ስለ ሀገራቸው ዘላቂ ሰላም ፣ ልማት ፣  ብዝሃነት ፣ ሀገራዊ አንድነትና ኢትዮጵያዊነት በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል ።

በስልጠናው ወጣቶች ራሳቸውን ፈልገው እንዲያገኙ፣   የነገ የህይወት መስመራቸውን እንዲለዩ እና ወገን ማገልገል  ክብር መሆኑን  እንዲረዱ ሰፊ ስራ ተሰርቷልም ነው ያሉት  ።

በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በቀጣይ የበጎ ፈቃድ ተግባር ለመስጠት በሚሰማሩባቸው አካባቢዎች  የተዋጣለት የበጎ ተግባር  ስራ መስራት የሚያስችላቸውን ስንቅ  በስልጠናው ማግኘታቸውን ገልፀዋል ።

የሰላም ሚኒስቴር የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ  የማህበረሰብ አገልግሎት  ፕሮግራምን በሀገር ደረጃ ቀርፆ መጀመሩ የተረጋጋችና ሰላሟ የተረጋገጠ  ሀገር ለመገንባት የጀመረውን መንገድ ማሳያ መሆኑን የስልጠናው አስተባባሪዎችና አሰልጣኞች  መናገራቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን https://play.google.com/store/apps/details… በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም 98.1 እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ፡፡ ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.