Fana: At a Speed of Life!

የቱሉ ቦሎ  – ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ወደ አሰፓልት ንጣፍ ስራ ተሸጋገረ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 3 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)  80 ኪሎሜትር የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ  – ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ወደ አሰፓልት ንጣፍ ስራ መሸጋገሩ ተገለጸ።

እስካሁን ባለው አፈጻጸም 26 ኪሎ ሜትሩ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍሎች አስፓልት ለማልበስ እየተሰራ ነው።

በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ ና የአፈር ሙሌት ፣ የቤዝ ኮርስ ስራ ፣ የአስፋልት እና  ፣ የድልድይ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ ነው።

በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የቱሉ ቦሎ – ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልልን ከአጎራባች የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ ፐሮጀክት ነው ተብሏል፡፡

ከቡታጂራ አዲስ አበባ ከሚወስደው አውራ መንገድ ጋርም በአቋራጭ ያስተሳስራል ፡፡

የቱሉ ቦሎ – ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር  በጀት መሆኑ ተመላክቷል።

3 ወረዳዎችን አቋርጦ ኬላ ከተማ የሚደርሰው ይህ መንገድ በአካባቢው በሚገኙ በገብስ ፤ ስንዴ ፤ ባቄላና አተር ምርቶቹ የታወቀ በመሆኑ ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማእከላዊ ገበያ እንዲደርስ ስለሚያስችል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያጎለብታል፡፡

የቱሉ ቦሎ – ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ አመት ለማጠናቀቅ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.