Fana: At a Speed of Life!

የአለም ባንክ የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለመደገፍ ለኢትጵዮያ 80 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአለም ባንክ በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለመደገፍ እና በአነስተኛ መሬት ለሚያርሱ ገበሬዎች የተሻለ አማራጭን ለመፍጠር 80 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አደረገ።

የአለም ባንክ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ የባንኩ አንድ አካል የሆነው አለም አቀፉ የልማት ማህበር ለኢትዮጵያ 80 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ እንዲያደረግ በትናትናው ዕለት ውሳኔ አሳልፏል።

ይህ ድጋፍ በዋነኝነት መንግስት የግብናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሻሻል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ እና በአነስተኛ መሬት የእርሻ ስራ ለሚያከናውኑ ገበሬዎች የገበያ እድል ለመፍጠር የሚውል ነው ተብሏል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.