Fana: At a Speed of Life!

የአሜሪካ የበጀት ጉድለት ወደ 3 ትሪሊየን ዶላር ከፍ አለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የዩናይትድ ስቴትስ የበጀት ጉድለት ወደ 3 ትሪሊየን ዶላር ከፍ ማለቱ ተነገረ።

የበጀት ጉድለቱን የሀገሪቱ የፌደራል መንግስት ለኮሮናቫይረስ ማገገሚያ ያዋለው ገንዘብ እንዳናረው ነው የተመለከተው”

የሀገሪቱ የገንዘብ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ባለፉት 11 ወራት የፌደራል መንግስቱ 6 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ያደረገ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 2 ትሪሊየን ዶላሩ ለኮሮናቫይረስ የኢኮኖሚ ጫና መከላከያ የዋለ ነው ።

እንደ ሪፖርቱ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከመከሰቱም በፊት የሀገሪቱ የበጀት ጉድለት ወደ 1 ትሪሊየን ዶላር ወደ መሆን እየተጠጋ ነበር ነው የተባለው።

በበጀት ዓመታቸው ማብቂያ ላይ የፌደራል መንግስቱ የበጀት ጉድለት 3 ነጥብ 3 ትሪሊየን ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፥ ይህም መጠን ከአምናው በሶስት እጥፍ የበለጠ ነው።

የሀገሪቱም አጠቃላይ እዳ 26 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር ይበልጣል ተብሎ ይጠበቃል ።

 

ምንጭ፦ ቢቢሲ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.