Fana: At a Speed of Life!

የአሮጌው ብር የመገበያያ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ያበቃል

አዲስ አበባ፣ ህዳር 21፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሮጌው ብር ኖት የመገበያያ ጊዜ ከነገ ህዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ያበቃል።

የአሮጌው ብር ኖት ቅያሬ ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል።

ባንኩ ከዚህ ቀደም ህዳር 10 ቀን 2013 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ከነገ ጀምሮ በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት አይቻልም።

ከመስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም አሮጌ የብር ኖቶች በአዲስ የብር ኖቶች እየተቀየሩ መሆኑ ይታወቃል።

የብር ኖት ቅያሬው በሶስት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ መወሰኑም አይዘነጋም።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.