Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴቬሎፕመንት ተገኝተው ማዕድ አጋሩ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴቬሎፕመንት ተገኝተው የገና በዓልን በማስመልከት ማዕድ አጋርተዋል።

ብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴቬሎፕመንት መንግስታዊ ያልሆነ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን፤ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ህይወት ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ነው።

በዚህም ኑሯቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ወጣቶች እና ሴተኛ አዳሪዎች ህይወትን በመቀየር ላይ በትኩረት የሚሰራ ነው።

በድርጅቱ ተገኝተው የማዕድ ማጋራት ያከናዉት አቶ መለሰ አለሙ የድርጅቱን ህይወታቸው የተለወጠ ወጣቶች መኖሪያና ክሊኒክ መጎብኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.