Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2013 (ኤፍ ቢሲ) በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማለፋን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት ።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሰው ፣የኢፌድሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር ፣ም/ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ እና ሌሎች የስፖርት ቤተሰቦች ተገኝተው ቡድኑን አበረታተዋል ።

ብሔራዊ ቡድኑ በነገው ዕለት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ከአረፋበት ሆቴል ተነስቶ በአዲስአበባ በተመረጡ ዋና ዋና ጎዳናዎች ለህዝቡ ደስታቸውን ይገልፃሉ ፤ ህዝቡም ለብሔራዊ ቡድኑ ያለውን ድጋፍ እና አክብሮት የሚገልፅ ይሆናል መባሉን ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.