Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በኡጋንዳ አቻው ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በኡጋንዳ አቻው ተሸነፈ፡፡

የኡጋንዳ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው አጋማሽ ሁለት በሁለተኛው አጋማሽ ደግሞ አንድ ግብ በማስቆጠር ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ያሸነፈው፡፡

በምድብ ኤ  ኢትዮጵያ ኡጋንዳን በመከተል ወደ ሚቀጥለው ዙር ማለፏን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታ፡፡

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአሰልጣኝ እንድሪያስ ብርሃኑ ይመራል፡፡

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.