የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀምራል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከወራት እረፍት በኋላ ዛሬ ይጀመራል፡፡
ሊጉ ዛሬ ሲጀምር ክሪስታል ፓላስ ከአርሴናል ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሼልስት ፓርክ ሰታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በመርሃ ግብሩ የመጀመሪያ ሳምንት በነገው እለት ስድስት ጨዋታዎችን የሚደረጉ ሲሆን ሊቨርፑል ከፉልሃም፣ቼልሲ ከኤቨርተን እንዲሁም ቶተንሃም ከሳውዝሃምፕተን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡