የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ለብርሃነ ጥምቀቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
በተመሳሳይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር የጥምቀትን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
“የዘንድሮው የጥምቀት በዓል ትልልቅ ድሎችን ባስመዘገብንበት እና ከፊት ለፊታችን የተጋረጡ ከባድ ፈተናወችን እየተጋፈጥን የምናከብረው በዓል በመሆኑ ከዚህ ቀደም ካከበርናቸው በዓላት ለየት ይላል” ብለዋል።
ወቅቱ ትላልቆቹን የጥፋት መሀንዲሶች በተባበረ ክንድ ድል የነሳንበት ቢሆንም የዘሩት የጥላቻ ዘር በአንዴድ ጊዜ ተነቅሎ የሚጠፋ ባለመሆኑ አሁንም ከውስጥም ከውጭም የተቀናጁ የጥፋት ሙከራወች እና ከባባድ ፈተናወች መኖራቸውንም አንስተዋል።
የጥምቀት በዓል ከሀይማኖታዊ ይዘቱ በተጨማሪ የክልሉን ገፅታ የበለጠ የሚገነባበትና በመሆኑም እንግዶችን በፍቅር ተቀብሎ በማስተናገድ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲሁም የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው በክልሉ የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የሕዝብ መጨናነቅን በመቀነስ እና ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ጥንቃቄ በማድረግ በዓሉን እንዲያከብሩም ጠይቀዋል።