የደብረብርሀን ከተማ ፖሊስ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኮ/ር ታዬ ሀብተጊዮርጊስ በቁጥጥር ስር ዋሉ
ከዚህ ጋር በተያያዘም ከተማ አስተዳደሩ ሁለት የፖሊስ አባላትን በተጨማሪነት በቁጥጥር ስር ማዋሉ አስታውቋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት የፖሊስ አባላት ከሽብር ቡድኑ ህወሓት ጋር ግንኑነት አላቸው ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች ከእስር እንዲፈቱ በማድረጋቸው ነው ተብሏል።
የደብረብረሀን ከተማ አስተዳድር ሰላምና ደህንነት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ በደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ኢንስፔክተር አዲስ ገብረህይወት እና ዋና ሳጅን ሙሉጌታ ጋሻው ናቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።