Fana: At a Speed of Life!

የፋና ላምሮት የድምጻውያን ውድድር በነገው ዕለት ይጀምራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፋና ላምሮት ልዩ የባለ ተሰጥዖ ድምጻዊያን ውድድር በነገው ዕለት ይጀምራል፡፡
 
በዚህ ውድድር ለይ ተሰጥዖና ልምድ ያላቸው እና ቅድመ ማጣሪያውን ያለፉ 24 ድምፃዊያን ይሳተፉበታል፡፡
 
ውድድሩ በሙሉ የሙዚቃ ባንድ እና በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት የሚተላለፍ ሲሆን ዳኝነቱም በሦስት ታዋቂ የሙዚቃ ሞያተኞች እና በተመልካች በሚሰጥ የኤስ ኤም ኤስ የድምፅ ውጤት ይዳኛል፡፡
 
ለስድስት ሳምንታት ብቻ ለሚካሄደው ውድድር 250ሺህ ብር ሽልማትም ተዘጋጅቷል፡፡
ፕሮግራሙ ዘውትር ቅዳሜ ከ 7፡00-10፡00 ሰዓት በፋና ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.