Fana: At a Speed of Life!

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በአፋር ክልል ሀገርን የማዳን ዘመቻ ለተሳተፉ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ታሳስ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በአፋር ክልል ሀገርን የማዳን ዘመቻ ለተሳተፉ ወገኖች የሚውል ከ580 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው የአይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡
የሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ቤተልሄም ዳኘ፥ ዲላ ዩኒቨርሲቲን ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመደበኛ ስራቸው ጎን ለጎን ሀገርን በማዳን ዘመቻው እያደረጉት ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ነው ያመለከቱት።
በቀጣይም በመቀናጀት የሀገርን እድገት፣ ሠላምና ብልፅግና በሚገነቡ ተግባሮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከሠመራ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.