Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር አብረሃም በላይ የወንጪ -ደንዲ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዶክተር አብረሃም በላይ የገበታ የወንጪ -ደንዲ  የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል።

ዶክተር አብረሃም  በላይ በጉብኝቱ ወቅትም÷ ከ3 ወራት በፊት የተጀመረው የፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ በተቀናጀ መንገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ከክረምት በፊትና በክረምት ወራት መሰራት ያለባቸው ስራዎች በእቅድ ተለይተው በመተግበር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የመሰረተ ልማት እና የወሰን ማስከበር ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

በፕሮጀክቱ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ለመሰማራት ባለሀብቶች ፕሮፖዛል እያቀረቡ መሆኑን ዶክተር አብርሀም ተናግረዋል።

አያይዘውም አሁንም ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ዶክተር አብረሃም በላይ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው  የወንጪ -ደንዲ ፕሮጀክት አስተባባሪ  መሆናቸው ይታወቃል።

በዙፋን ካሳሁን

ፎቶ ከኢዜአ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.