Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር እሌኒ ገብረመድህን የተመድ የልማት ፕሮግራም የአፍሪካ ዋና የፈጠራ ስራ ኃላፊ በመሆን ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞ የኢሴክስ መስራች ዶክተር እሌኒ ገብረመድህን የተመድ የልማት ፕሮግራም (ዩ ኤን ዲ ፒ) የአፍሪካ ዋና የፈጠራ ስራ ኃላፊ በመሆን ተሾሙ፡፡

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅትን (ኢ.ሲ.ኤክስ) እንዲሁም ብሉ ሙን የተሰኙ ተቋማትን በመመስረት እና በመምራት የሚታወቁት ዶክተር እሌኒ ለዚህ አዲስ ስራቸው ወደ ኒውዮርክ እንደሚያቀኑ ይጠበቃል፡፡

በአፍሪካ ውስጥ የወጣቶች የፋይናንስ ፈጠራ አብዮት ቲምቡኮትን በማስጀመር ግንባር ቀደም ሚና እንደሚጫወቱ ዩኤንዲፒ በድረ ገጹ ማስነበቡን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የአፍሪካን የወደፊት ዕጣ ፈንታ፣ ዲጂታላይዜሽንን ማሳደግ እና ወጣቶችን ማበረታታት ትኩረት አደርገው ይሰራሉ ብዩ አምናለሁ ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ረዳት ዋና ጸሐፊ እና የዩ.ኤን.ዲ. ፒ የአፍሪካ ቀጠና ዳይሬክተር አሁንና ኢዚያኮንዋ ገልጸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.