Fana: At a Speed of Life!

ጀርመን ለኢትዮጵያ የ80 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ እርዳታ እንደምትሰጥ ይፋ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጀርመን ለኢትዮጵያ የ80 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ እርዳታ እንደምትሰጥ ይፋ አደረገች፡፡

የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር አቶ አህመድ ሺዴ ትናንት ታህሳስ 8 2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደርን አውር ስቴፓንን ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

በዚህም ወቅት በሁለቱ አገራት የኢኮኖሚ ልማት ትብብር ላይ የተወያዩ ሲሆን ÷ አምባሰደሩ ጀርመን ለኢትዮጵያ የ80 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ እንደምታደርግ ይፋ አድርገዋል፡፡

የገንዘብ ድጋፉ ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም፣ ለመልካም አስተዳደር፣ ለመሬት አጠቃቀም፣ ለግብርና ሜካናይዜሽን እንዲሁም ድርቅን ለመቋቋም ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች የሚውል መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.