Fana: At a Speed of Life!

ግብፅ በኢትዮጵያ ከገጠማት መራር ሽንፈት በኋላ አሰልጣኟን አሰናበተች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብፅ እግር ኳስ ማህበር የብሄራዊ ቡድኑን አሰልጣኝ ኢሀብ ጋላልን ከአሰልጣኝነት አሰናበተ።

ግብጽ የዛሬ ሳምንት ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዋን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከጨዋታ ብልጫ ጋር 2 ለ 0 መሸነፏ ይታወሳል።

ከዚህ ባለፈም በወዳጅነት ጨዋታ ከትናንት በስትያ በደቡብ ኮሪያ የ4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዳለች።

ከደቂቃዎች በፊት ይፋ በሆነው መረጃ መሰረት ደግሞ የሀገሪቱ የእግር ኳስ ማኅበር የብሔራዊ ቡድኑን አሠልጣኝ ከመንበሩ ማንሳቱን ይጠቁማል።

የ54 ዓመቱ አሠልጣኝ ቡድኑን ከተረከቡ 2 ወር ያልሞላቸው ቢሆንም በኢትዮጵያ የደረሰባቸው ሽንፈት መንበራቸው እንዲንገጫገጭ ማድረጉን ሶከር ኢትዮጵያ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.