ጠ/ሚ ዐቢይ ከተመድ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር በስልክ ተወያዩ፡፡
በውይይታቸው የአንበጣ መንጋ የሚያደርሰውን ጥቃት መከላከል በሚቻልበት አግባብ ላይ መወየታቸውን በፌስቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡
እንዲሁም ተያያዥ ተፅዕኖዎች እና ስለ አፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ የሰላም እና መረጋጋት ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ነው ያስታወቁት።