Fana: At a Speed of Life!

ጣሊያን በተለያዩ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጣሊያን በተለያዩ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጻለች፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ የደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን ከጣሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዊጂ ዲ ማዮ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

በውይይታቸውም ሉዊጂ ዲ ማዮ ጣሊያን በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት በሚያስፈልግባቸው ሥፍራዎች እንዲደርስ እና አካታች ብሔራዊ ምክክር እንዲካሄድ እያደረገች ያለውን ያላሰለሰ ጥረት ጣሊያን እንደምታደንቅ መግለጻቸውንም በኢትዮጵያ ከጣሊያን ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.