Fana: At a Speed of Life!

ፋውዚያ ዩሱፍ በፕሬዚዳንትነት ለመወዳደር ለሶማሊያ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቀረቡ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያ የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ፋውዚያ ዩሱፍ ሀጂ አደም በሶማሊያ በሚካሄደው ቀጣይ ምርጫ ለፕሬዚዳንትነት ለመወዳደር የዕጩነት ጥያቄ አቀረቡ፡፡

የሀገሪቷ ምርጫ ቦርድም ጥያቄያቸውን ከተቀበለው በሶማሊያ የምርጫ ታሪክ ለከፍተኛ አመራርነት ጥያቄ ያቀረቡ ሁለተኛዋ ሴት ይሆናሉም ነው የተባለው፡፡

በፈረንጆቹ 2004 አሻ አህመድ አብደላ በሀገሪቷ ፓርላማ ውስጥ ለከፍተኛ አመራርነት ተወዳድረው ያላለፉ የመጀመሪያዋ የሴት ዕጩ እንደነበሩ ዘ ኢስት አፍሪካን አስታውሷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.