Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ቃለ መሃላ ፈጸሙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ቃለ መሃላ ፈጸሙ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ለቀጣዮቹ ስድስት አመታት ሃገራቸውን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ዛሬ በይፋ ቃለ መሀላ ፈጽመዋል፡፡

ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር በተካሄደው ምርጫ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

በዛሬው እለትም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች በተገኙበት በይፋ በአለ ሲመታቸው ተከናውኖ ቃለ መሀላ ፈጽመዋል፡፡

በበዓለ ሲመቱ ወቅት በመዲናዋ ካምፓላ ከፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የፀጥታ አካላት ጠንካራ ቁጥጥር እንደነበር ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል፡፡

ከትናንት በስቲያ ሰኞም በዓለ ሲመቱን ለማወክ አቅደዋል የተባሉ ከ40 በላይ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.