Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ 31 አዳዲስ ሚኒስትሮችን ሾሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 2 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ 81 አዳዲስ የካቢኔ አባላቶቻቸውን ይፋ አደረጉ፡፡

ፕሬዚዳንቱ 31 አዳዲስ ሚኒስትሮች እና 50 ምክትሎቻቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

ከአዳዲስ ተሿሚዎች ውስጥ ከ10 የሚበልጡ ሴት ተሿሚዎች ይገኙበታል፡፡

ከእነዚህ መካከል የቀድሞዋን የሃገሪቱ የትምህርት ሚኒስትር ጄሲካ አሉፖ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርገው ሲሾሙ፥ ሮቢናህ ናባንጃን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯን ጨምሮ በከፍተኛ የሃላፊነት ቦታዎች ላይ ሴት ሚኒስትሮች መሾማቸውን የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል፡፡

በርካታ የቀድሞ ሚኒስትሮችና የካቢኔ አባላት በአዲሱ የፕሬዚዳንቱ ሹመት ውስጥ አልተካተቱም፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.