Fana: At a Speed of Life!

የኢንዶኔዢያው ፕሬዚዳንት ጆኮዊ በሩሲያና ዩክሬን ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዶኔዢያ ፕሬዚዳንት ጆኮዊ ሩሲያንና ዩክሬንን ሊጎበኙ ነው።

በጉብኝታቸው የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ስንዴ ወደ ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ ለማሳመን ጥረት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ሩሲያ እንደሚጓዙ የዘገበው ጃካርታ ፖስት፥ ወደ ዩክሬን እና ሩሲያ ከማቅናታቸው በፊት በሚቀጥለው ሳምንት በጀርመን በሚካሄደው የቡድን 7 ስብሰባ ላይ እንደሚታደሙም አስታውሷል፡፡

በጉብኝታቸው በመጭው ህዳር ወር ኢንዶኔዢያ በምታስተናግደው የቡድን 20 አባል ሃገራት ስብሰባ ጉዳይ ላይ ከፑቲን ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.