Fana: At a Speed of Life!

ሊቨርፑል ከ30 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሊቨርፑል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ፡፡

የአንፊልዱ ክለብ ትናንት ምሽት ተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በቼልሲ መሸነፉን ተከትሎ ከ30 አመት በኋላ ሻምፒዮንነቱን አውጇል፡፡

የክለቡ ደጋፊዎችና ተጫዋቾች ከረጅም አመታት በኋላ የተገኘውን ድል አክብረውታል፡፡

አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ሁኔታዎች ሲመቻቹ ከደጋፊዎች ጋር ድሉን ስለማክበር እንደሚያስቡ ተናግረዋል፡፡

ትናንት ምሽት በተደረጉ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በርንሌይ ዋትፎርድን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

አርሰናል ከሜዳው ውጭ ሳውዝሃምፕተንን 2 ለ 0 አሸንፎ ተመልሷል፡፡

በምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ ደግሞ ቼልሲ ማንቼስተር ሲቲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በቀጣዩ አመት የቻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎን ለማሳካት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.