Fana: At a Speed of Life!

ማሊያዊቷ እናት በአንድ ጊዜ 9 ልጆችን ተገላገለች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የማሊ ዜግነት ያላት እናት በአንድ ጊዜ ዘጠኝ ልጆችን መገላገሏ ተሰምቷል፡፡

ሃሊማ ሲሼ የ25 ዓመት ወጣት ማሊያዊ ስትሆን፤ በሞሮኮ ሃገር ሆስፒታል ዘጠኝ ልጆችን መገላገሏን የማሊ ጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ወጣቷ 7 ልጆችን እንደምትወልድ በአልትራሳውንድ መመርመሪያ ታይቶ ስትጠበቅ የነበረ ቢሆንም፤ አምስት ሴቶችና አራት ወንዶችን በሰላም መገላገል እንደቻለች ተነግሯል፡፡

በአሁኑ ወቅትም እናት እና የተወለዱት ልጆች በሙሉ ጤና ላይ እንደሚገኙም ዶክተር ሲቤ የገለጹ ሲሆን፤ ከጥቂት ሳምንታት በኋላም ከሆስፒታል ይወጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.