Fana: At a Speed of Life!

ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሦስት ዓመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 13 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሶስት አመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ።

የ52 አመቱን አሰልጣኝ ሊራዘም በሚችል የአንድ አመት ተጨማሪ ኮንትራት ለሶስት አመታት ከሆላንዱ አያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

የእንግሊዙ ክለብ አሰልጣኙን ማስፈረሙን ተከትሎ ለአያክስ የኮንትራታቸውን ማካካሻ የሚከፍል ይሆናል።

አዲሱ አሰልጣኝ በውጤት ቀውስ የሚገኘውን ክለብ መልሶ የመገንባት ቀዳሚ ስራ ይጠብቃቸዋል ተብሏል።

የላንክሻየሩ ክለብ ከአሰልጣኝ አሌክስ ፈርጉሰን መልቀቅ በኋላ የሊግ ዋንጫ አሸንፎ አያውቅም።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.