Fana: At a Speed of Life!

ምዕራባውያን ሩሲያን ከዓለም ኢኮኖሚ ለማግለል የሚያደርጉት ጥረት አይሳካም – ፕሬዚዳንት ፑቲን

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በምዕራባውያኑ ተፅዕኖ ከዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ መድረክ ለቃ እንደማትወጣ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስታወቁ ።

ፕሬዚዳንት ፑቲን በበይነ መረብ በተካሄደው የአውሮፓ እና እስያ ሀገራት የኢኮኖሚ ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር፥ ሩሲያን በማዕቀቦች ለመጉዳት እና ለማዳከም የሚሹ ሀገራት እንደማይሳካላቸው ይወቁት ፤ ይልቁንም የሚጎዱት እራሳቸውን ነው ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ፑቲን “ማዕቀቦቹ በአንዳንድ ምክንያቶች እንዲያውም አጠንክረውናል” ማለታቸውን አር ቲ ኒውስ ዘግቧል፡፡

ሀገራት ከእኛ ተሞክሮ ልምድ ወስደው በየትኛውም ሀገር ላይ ጥገኛ ያልሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መቅረፅ እና ነጻነታቸውን ማወጅ አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.