በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሐዋሳ ከተማ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሐዋሳ ከተማ ድል ቀንቶታል።
ረፋድ ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሐዋሳ ከተማ መከላከያን 2 ለ 1 አሸንፏል።
መከላከያ በተሾመ በላቸው ጎል ጨዋታውን መምራት ቢችልም፥ ሐዋሳ ከተማ በብሩክ በየነ እና ወንድአገኝ ሐይሉ ጎሎች 2 ለ 1 ማሸነፍ ችሏል።
ከሰአት በኋላ በተካሄደ ሁለተኛ ጨዋታ ደግሞ አዳማ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል።