Fana: At a Speed of Life!

በናይጀሪያ እስካሁን 51 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ገለጹ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የናይጀሪያው ፕሬዚዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ ከሰሞኑ በሃገሪቱ በተፈጠረው አለመረጋጋት 51 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን ገለጹ፡፡

ፕሬዚዳንቱ የፖሊስን የሃይል እርምጃ በመቃወም በተካሄደው ሰልፍ ላይ የፀጥታ አካላት በወሰዱት እርምጃ በርካቶች መቁሰላቸውንም ገልጸዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ 11 የፖሊስ አባላት እና ሰባት ወታደሮችም ለህልፈት ተዳርገዋል ነው ያሉት፡፡

በሃገሪቱ ያለውን ሁኔታ እየተከታተሉ ያሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ደግሞ የፀጥታ አካላት ሰልፈኞች ላይ በመተኮስ በጥቂቱ 12 ንጹሃንን ገድለዋል ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል፡፡

ቡሃሪ ከአሁን እና የቀድሞ ባለስልጣናት ጋር በሃገሪቱ ከተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ለመምከር በተቀመጡበት ወቅት በሰጡት መግለጫ በጥቂቱ 37 ንጹሃን መቁሰላቸውንም ተናግረዋል፡፡

በስብሰባው ወቅት በሰጡት መግለጫ ፕሬዚዳንቱ በፀጥታ አካላት የተወሰደውን እርምጃ አለማውገዛቸውም ነው የተሰማው፡፡

በወቅቱ መንግስት ህግና ስርአትን እንደሚያስከብርና ስርአት አልበኝነትን አይፈቅድም ማለታቸው የሃገሬውን ዜጎች አላስደሰተም፡፡

በናይጀሪያ የፀጥታ አካላት በሚወስድት ያልተመጣጠነ እና አሰቃቂ እርምጃ ሳቢያ ተደጋጋሚ ትችት ይቀርብባቸዋል፡፡

ከሰሞኑም ይህን የሚኮንን ሰልፍ የተጠራ ሲሆን፥ ተቃውሞው ወደ አመጽና ብጥብጥ እየተቀየረ ስለመሆኑም ይነገራል፡፡

ምንጭ፥ አልጀዚራ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.