Fana: At a Speed of Life!

በአውሮፓ ዋንጫ ዌልስ እና ስዊዘርላንድ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 5 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2020 የአውሮፓ ዋንጫ ዛሬ አንድ ጨዋታ አስተናግዷል፡፡

በአዘርባጃን ባኩ ከተማ የተካሄደው ጨዋታ በምድብ 1 የተደለደሉት ዌልስ እና ስዊዘርላንድን አገናኝቷል፡፡

ጨዋታው አንድ አቻ ሲጠናቀቅ ሙር ለዌልስ እንዲሁም ኢምቦሎ ለስዊዘርላንድ ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡

ውድድሩ ትናንት ምሽት ሲጀመር በምድቡ ሮም ላይ ቱርክ ከጣሊያን ተጫውተው ጣሊያን 3 ለ 0 በማሸነፍ ውድድሩን በጥሩ ሞራል ጀምረዋለች፡፡

በምሽቱ ጨዋታ የቱርኩ ተከላካይ ደሚራል በራሱ መረብ ላይ እንዲሁም ቺሮ ኢሞቢሌ እና ኢንሴኜ ለጣሊያን የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.