Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ 21 ወለሎች ያሉት የመኖሪያ አፓርታማ ሊገነባ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ 21 ወለሎች ያሉት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ሊገነባ ነው።

የመኖሪያ አፓርታማው ሮክስቶን እና ሂሆንግ ተሰኙ ድርጅቶች ለአካባቢ ተስማሚ ሆነው እንደሚገነቡ ተነግሯል።

አፓርታማው ሲግናል አካባቢ እንደሚገነባ የተነገረ ሲሆን ከፍታ የተሰኘ ስም ተሰጥቶታል።

ለአፓርታማ ግንባታው በቢሊየኖች ብር ወጪ እንደሚደረግበት እና በፈረንጆቹ 2023 እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

የግንባታው ዲዛይን  የኢትዮጵያ ሀብት የሆኑ ታሪካዊ ቅርሶች መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነም ተነግሯል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.