Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 40 ሺህን ተሻግሯል

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 17፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 20 ሺህ 153 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 1 ሺህ 638 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ይህንንም ተከትሎ በሀገሪቱ በአጠቃላይ እስካሁን ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 40 ሺህ 671 ደርሷል።

በሌላ በኩል 515 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 14 ሺህ 995 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

በ24 ሰዓታት ውስጥም 16 ሰዎች በቫይረሱ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ 678 ሰዎች እስካሁን ህይወታቸውን አጥተዋል።

በአሁኑ ወቅት 291 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በፅኑ የታመሙ መሆናቸውንም ሚኒስቴሩ በእለታዊ ሪፖርቱ አመልክቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.