Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሽግግር ተግዳሮቶችን በተመለከተ በባህርዳር ከተማ ውይይት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥር 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሽግግር ተግዳሮቶችን በተመለከተ በባህርዳር ከተማ ውይይት እየተደረገ ነው።

በውይይቱ ላይ ምሁራን፣ የፖለቲካ ፖርቲዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎችና ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ የህዝብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

ውይይቱ በትናንትናው እለት ከተጀመረው የምክክር መድረክ የቀጠለ ነው።

በዛሬው እለትም የሽግግር ፅንሰ ሀሳብን ጨምሮ በኢትዮጵያ የተደረጉ የሽግግር ሙከራዎች እና አሁን ላይ ያለው ሽግግር እንደ ሀገርና እንደ ህዝብ ያለውን መልካም አጋጣሚዎች በተመለከተ የውይይት መነሻ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል ።

በትዝታ ደሳለኝ

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.