በኦሮሚያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ከኅዳር 30 እስከ ታኅሣሥ 2 ቀን ይሰጣል
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልል ደረጃ የሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና በኦሮሚያ ክልል ከኅዳር 30 እስከ ታኅሣሥ 2 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ከመዋዕለ ሕፃናት ውጭ ያለው የመማር ማስተማር ሂደትም የፊታችን ሰኞ ይጀምራል ተብሏል፡፡
የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት መጀመሪያ ጊዜ ለሁለት ሳምንታት መራዘሙንም ቢሮው አስታውቋል፡፡