Fana: At a Speed of Life!

በዩሮፓ ሊግ ሲቪያ እና ሻካታር ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተካሄደዋል፡፡

በጀርመን እየተደረገ ባለው ውድድር የስፔኑ ሲቪያ እና የዩክሬኑ ሻካታር ዶኔስክ ግማሽ ፍጻሜ መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ከእንግሊዙ ወልቨርሃምፕተን ወንደረርስ ጋር የተጫወተው ሲቪያ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

በጨዋታው ወልቭሶች አዳማ ትራኦሬ ተጠልፎ ያገኙትን የፍጹም ቅጣት ራውል ጂሜኔዝ አባክኖታል፡፡

ለሲቪያ ኦካምፖስ በጨዋታው መጠናቀቂያ ላይ የማሸነፊያዋን ጎል አስቆጥሯል፡፡

በሌላ ጨዋታ ሻካታር ዶኔስክ ባዜልን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎታል፡፡

ለሻካታር ሞራኤስ፣ ታይሰን፣ ሎሬንኮ እና ዶስ ሳንቶስ የድል ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ወልፍስዊንከል ለባዜል ማስተዛዛኛዋን አስቆጥሯል፡፡

በግማሽ ፍጻሜው ሲቪያ ከማንቼስተር ዩናይትድ እንዲሁም ሻካታር ከኢንተር ሚላን ይገናኛሉ፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.