Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ አፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከግማሽ ሚሊየን አልፏል

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 27፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከግማሽ ሚሊየን መብለጡ ተገለፀ፡፡

በሃገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 511 ሺህ 485 የደረሰ ሲሆን ÷8 ሺህ 366 ሰዎችም ለህልፈት ተዳርገዋል ነው የተባለው፡፡

በዚህም ከአፍሪካ ቀዳሚ ስትሆን ግብፅ፣ናይጄሪያ እና ጋና ተከታዩን ደረጃ ይይዛሉ፡፡

በግብፅ 94 ሺህ 483 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 4 ሺህ 865 ሰዎች በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

በናይጄሪያ ደግሞ 43 ሺህ 841 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን÷ 888 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ነው የተባለው፡፡

እንዲሁም በጋና 37 ሺህ14 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው 182 የሚሆኑት ለህልፈት መዳረጋቸው ታውቋል፡፡

እንደ ወርልድ ኦ ሜትር መረጃም በአጠቃላይ በአፍሪካ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ1 ሚሊየን የተጠጋ ሲሆን በቫይረሱ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥርም 20 ሺህ 350 ደርሷል፡፡

#FBC

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.