በዳሬሰላም ለሚካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ስፍራው አቀና
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በታንዛኒያ ዳሬሰላም ለሚካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ ከ20 እና ከ18 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው የአትሌቶች ልዑክ ዛሬ ማለዳ ወደ ስፍራው አቅንቷል፡፡
የልዑካን ቡድኑ÷ 27 አትሌቶችን ያካተተ መሆኑን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉት አትሌቶችም÷ ከ100 ሜትር ጀምሮ እስከ 5 ሺህ ሜትር እንዲሁም የሜዳ ተግባራትን ጨምሮ በአጠቃላይ በ20 የውድድር አይነቶች በሁለቱም ፆታ የሚካፈሉ ይሆናል፡፡