Fana: At a Speed of Life!

በግዥ ዕቅድና ንብረት አስተዳደር በሚታዩ ክፍተቶች ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) “ግዥን በዕቅድ በመምራት የንብረት አስተዳደርን ውጤታማነት እናሳድግ” በሚል መሪ ቃል በግዥ ዕቅድና ንብረት አስተዳደር በሚታዩ ክፍተቶች ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር እያደረገ ያለው ውይይት በገንዘብ ሚኒስቴር አዳራሽ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡

የውይይት መድረኩ በመንግሥት ግዥ ዕቅድና ንብረት አስተዳደር በሚታዩ ክፍተቶች ላይ ያተኮረ ነው።

በመድረኩም ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ፣ ግብርና ሚኒስቴር፣ ማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲና ሌሎች የፌዴራል ተቋማት ተሳታፊ መሆናቸውን አብመድ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.