Fana: At a Speed of Life!

በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሚመራ የልዑካን ቡድን ጁባ ገባ

አዲስ አበባ ፣መስከረም 23 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሚመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል።

የልኡካን ቡድኑ ጁባ የገባው በሱዳን የሽግግር መንግስትና በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል የሚፈረመው የሰላም ስምምነት  ላይ ለመታደም ነው።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጁባ ሲደርሱ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ለአንድ ዓመት ያህል ሁለቱን ቡድኖች ሲያደራድሩ መቆየታቸውን ከኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.