Fana: At a Speed of Life!

ባለፉት 24 ሰዓታት 915 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ11 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ8 ሺህ 957 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 915 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

በዚህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 17ሺህ 530 የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ቫይረሱ ያለባቸው 10 ሺህ 304 ሰዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት 138 ፅኑ ታማሚዎች የሚገኙ ሲሆን 187 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል።

ይህን ተከትሎም ከቫይረሱ ያገገሙት ሰዎች ቁጥር 6 ሺህ 950 እንደደረሰም ነው ሚኒስትሯ ያስታወቁት።

እንዲሁም በ24 ሰዓታት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የ11 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

በኢትዮጵያ እስካሁን በቫይረሱ ምክንያት 274 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

በአጠቃላይ ለ422ሺህ 354 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.