Fana: At a Speed of Life!

ቼልሲ ቲያጎ ሲልቫን አስፈረመ

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ብራዚላዊው ተከላካይ ቲያጎ ሲልቫ የእንግሊዙን ቼልሲ ተቀላቀለ፡፡

ሲልቫ ለምዕራብ ለንደኑ ክለብ የማራዘም አማራጭ ያለው የአንድ አመት የኮንትራት ፊርማውን አኑሯል፡፡

የ35 አመቱ ተከላካይ ሰማያዊዎቹን በነጻ ዝውውር ከፈረንሳዩ ፒ ኤስ ጂ ተቀላቅሏል፡፡

ሲልቫ በዘንድሮው ክረምት የቼልሲ አራተኛው ፈራሚ ሆኗል፡፡

ከእርሱ ቀደም ብሎ ቲሞ ዌርነር፣ ሃኪም ዛይች እና ቤን ቺልዌል ስታምፎርድ ብሪጅ ደርሰዋል፡፡

ክለቡ የማላንግ ሳርን ዝውውርም ማጠናቀቁ ተነግሯል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.