Fana: At a Speed of Life!

ናይጀሪያዊቷ ኢውያላ የመጀመሪያዋ ሴትና አፍሪካዊ የአለም ንግድ ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራል ሆኑ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ናይጀሪያዊቷ ንጎዚ ኦኮንጆ ኢውያላ የመጀመሪያ ሴትና የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ የአለም ንግድ ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራል ሆነው ተሹመዋል።

የአዲሷ ናይጀሪያዊት የአለም ንግድ ድርጅት ጄኔራል ዳይሬክተርነት ሹመት የፀደቀው የድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ልዩ ስብሰባ አድርጓ ስምምነት ላይ ከደረሰ በኋላ ነው።

የቀድሞ የናይጀሪያ የገንዘብ ሚኒስቴር ዶክተር  ንጎዚ ኦኮንጆ ኢውያላ የአለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርም ሆነው ያገለገሉ ሲሆን የአሜሪካ ዜግነት እንዳላቸው ቢቢሲ ዘግቧል።

የአለም ንግድ ድርጅት በአሁን ወቅት በሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ግጭት፣ ሀገራት እርስ በርሳቸው ታሪፍ መጣላቸው እና  የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያስከተለው የኢኮኖሚ ችግር መፍትሄ ሊሰጣቸው የሚገቡ ፊት ለፊቱ የተደቀኑ ተግዳሮቶች መሆናቸው ይነገራል።

አንድንድ ተንታኞችም የአለም ንግድ ድርጅት በአሁን ወቅት ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ይናገራሉ።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን https://play.google.com/store/apps/details… በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም 98.1 እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ፡፡ ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.