አምባሳደር ተሾመ በቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጋር መከሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ው ፔንግ ጋር መክረዋል።
ውይይታቸው በሁለትዮሽ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ እና የጋራ በሆኑ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ነበረ።
አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ለአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ፣ ስለ ኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳይ እና የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!