Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከአፍሪካ አምባሳደሮች ተጠሪ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከአፍሪካ አምባሳደሮች ተጠሪ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ አምባሳደር አዳራሂም አብዱላዬ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በኢትየጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡

በተጨማሪም በትግራይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተመለከተ እየተደረገ ስላለው ዝግጅት ፣ ስለ ህዳሴ ግድብ እና ኢትዮ-ሱዳን ጉዳይ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

አምባሳደር አዳራሂም አብዱላዬ በበኩላቸው ስለተደረገላቸው ገለጻ አመስግነው፥ የኢትዮጵያ መንግስት የውስጥ ችግሩን በራሱ አቅም ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይም በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለመፍታት የኢትዮጵያ መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚደግፉ ጠቅሰው፥ ከድንበር ጋር ያለውን ችግር በድርድር መፍታት አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.