Fana: At a Speed of Life!

አትሌት ፀሐይ ገመቹ በሊዝበን ግማሽ ማራቶን ድል ተቀዳጀች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አትሌት ፀሐይ ገመቹ በፖርቹጋል ዋና ከተማ ሊዝበን በተካሄደው የግመሽ ማራቶን ውድድር ለሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች፡፡

አትሌቷ የሊዝበንን ግማሽ ማራቶን ርቀት 1 ሰዓት ከ06 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጎይተይቶም ገብረ ስላሴ 1 ሰዓት ከ06 ደቂቃ 45 ሴኮንድ በመግባት 3ኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.