Fana: At a Speed of Life!

አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ከክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ከክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር ተወያዩ።

ቋሚ ኮሚቴዎቹ በበጀት ዓመቱ በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን አፈፃፀም ጎብኝተዋል፡፡

ኮሚቴዎቹ የልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም አስመልክተው ለርዕሰ መስተዳድሩ ገለፃ ማድረጋቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.